ማንነታችን
የፍራንክፈርት ኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን፣ የእግዚአብሔርን አምላክነት፣ የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝነትና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በመመስከር፣ በፍራንክፈርትና አካባቢዋ የእግዚአብሔርን መንግሥት ላለፉት 35 ዓመታት ስታሰፋ የቆየች ቤተ ክርስቲያን ናት። ዓላማችን ያላመኑት በክርስቶስ አምነው እንዲድኑ፣ ያመኑት ደግሞ በእግዚአብሔር ጸጋ ይበልጥ እንዲያድጉና በእምነታቸው እንዲጸኑ በትጋት ማገልገል ነው።
ይህን ታላቅ አደራ በትጋት እንድንወጣ ላለፉት 35 ዓመታት የረዳንን እግዚአብሔርን ከልብ እያመሰገንን፣ ከፊታችን ላለው የአገልግሎት ዘመንም የእግዚአብሔርን መንግሥት ይበልጥ ለማስፋፋት በላቀ ትጋት እየሠራን እንገኛለን።
ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበልነውን ይህን አደራና ኃላፊነት የምንተገብርበት ዋነኛ መመሪያችን፣ የሕያው እግዚአብሔር ቃል የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ነው።
Wer wir sind
Die Äthiopische Evangelische Gemeinde Frankfurt ist eine Gemeinde, die seit 35 Jahren das Reich Gottes in Frankfurt und Umgebung ausbreitet, indem sie die Gottheit Gottes, die Rettung durch unseren Herrn Jesus Christus und das Wirken des Heiligen Geistes bezeugt.
Es ist unser tiefstes Anliegen und unser fleißiger Dienst, dass Menschen, die noch nicht glauben, zum rettenden Glauben finden, und dass die Gläubigen in der Gnade Gottes wachsen und in ihrem Glauben gefestigt werden. Voller Dankbarkeit gegenüber Gott, der uns in den vergangenen 35 Jahren geholfen hat, diesen großen Auftrag treu zu erfüllen, arbeiten wir mit noch größerer Hingabe daran, Sein Reich auch in der vor uns liegenden Zeit weiter auszubreiten.
Unsere wichtigste Richtschnur zur Erfüllung dieses Auftrags, den wir von Christus empfangen haben, ist die Bibel – das lebendige Wort Gottes.
